1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ከሱዳን ወደ ኢትዮጵያ የሚሰደዱት ቁጥር ጨምሯል

ረቡዕ፣ ነሐሴ 24 2015

የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ ጉዳዩች ማስባበርያ ቢሮ OCHA የሱዳን ግጭት በኢትዮጵያ ላይ የሚያደርሰውን ተጽእኖ አስመልክቶ ባወጣው መረጃ በአሁኑ ወቅት በተለያዩ መንገዶች ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ሰዎች ቁጥር መጨመሩን አስታወቀ። በመተከል ዞን ጉባ ወረዳ በኩል ደግሞ ከ17ሺህ በላይ ከኢትዮጵያ ወደ ሱዳን የተፈናቀሉ ዜጎች መመለሳቸው ተገልጿል።

https://p.dw.com/p/4VlNR
 ፎቶ ከማኅደር፤ ቻድ ውስጥ የተጠለሉ የሱዳን ስደተኞች
የተባበሩት መንግሥታቱ ድርጅት የሰብአዊ ጉዳዩች ማስተባበሪያ ቢሮ ከሱዳን 76,500 የሚደርሱ ዜጎች የእርስ በርስ ግጭቱን በመሸሽ ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን ገልጿል። ፎቶ ከማኅደር፤ ቻድ ውስጥ የተጠለሉ የሱዳን ስደተኞች ምስል MOHANED BELAL/AFP

ከሱዳን ወደ ኢትዮጵያ የሚሰደዱት ቁጥር ጨምሯል

የተባበሩት መንግሥታቱ ድርጅት የሰብአዊ ጉዳዩች ማስተባበሪያ ቢሮ (UN OCHA) እንዳስታወቀው 76,500 የሚደርሱ ዜጎች የሱዳን እርስ በርስ ግጭት በመሸሽ ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል። ከሱዳን የሚሻገሩ ዜጎች በመተማ እና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በኩል በየጊዜው እየገቡ እንደሚገኙ ዘገባው ጠቅሷል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኩርሙክ በኩል ለገቡ 7,600 የሚደርሱ የሱዳን ዜጎች ሰብአዊ ድጋፍ መስጠቱን ድርጅቱ አስታውቋል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ መሐመድ አብዱላዚዝ በኩርሙክ ለሚገኙ 13,625 የሱዳን ስደተኞች እንደሚገኙ ተናግረዋል። በመተከል በኩል ደግሞ ወደ ሱዳን ተፈናቅለው የነበሩ 17,474 የኢትዮጵያ ዜጎች መመለሳቸውን አክለዋል።

የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ ጉዳዩች ማስባበርያ ቢሮ የሱዳን ግጭት በኢትዮጵያ ላይ የሚያደርሰውን ተጽእኖ አስመልክቶ ባወጣው መረጃ በአሁኑ ወቅት በተለያዩ መንገዶች ወደ ሀገሪቱ የሚገቡ ሰዎች ቁጥር መጨመሩንም ጠቁመዋል። ከ50 አስከ 60 የሚደርሱ ሰዎች በየጊዜው ወደ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኩርሙክ ወረዳ  እንደሚገቡም ተገልጸዋል። ወራትን ያስቆረውን የሱዳን ጦርነትን በመሸሽ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኩርሙክ በኩል ለገቡ 7,200 የሱዳን ዜጎች የምግብ ድጋፍ ማድረጉን ሰብአዊ ጉዳዎች ማስተባበሪያ ቢሮው አስታውቀዋል። 300 የሚሆኑ ስደተኞች እና የጥገኝነት ጠያቂዎችም በአሶሳ ዞን ሸርቆሌ የሚባል ወረዳ ውስጥ እንደሚገኙ ጠቁመዋል። በኩርሙክ በወባ በሽታ  የሕጻናት ሕይወት ማለፉን የመንግሥታቱ ድርጅት ዘገባ ያመለክታል።

ፎቶ ከማኅደር፤ የሱዳን ጦር አባል ዋና ከተማ ኻርቱም ውስጥ በውጊያ ላይ
ሱዳን ውስጥ ያልበረደው ውጊያ በሺህዎች የሚገመቱ የሀገሪቱን ዜጎች ለስደት እየዳረገ ነው። ፎቶ ከማኅደር፤ የሱዳን ጦር አባል ዋና ከተማ ኻርቱም ውስጥ በውጊያ ላይ ምስል @SUDANESEARMY1/UGC/AFP

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር መሐመድ አብዱላዚዝ  በሱዳንውስጥ ግጭት ከተከተሰ ጊዜ አንስቶ እስካሁን ወደ ኩርሙክ ወረዳ የገቡ ከ13 ሺህ በላይ እንደሆኑ ተናግረዋል። በኩርሙክ የሚገኙ የሱዳን ዜጎች መካከል የተወሰኑት ለምግብ እጥረት ተጋልጠው መቆየታቻቸውን እንዲሁም የወባ በሽታ መስፋፋት ጉዳት ማድረሱን አብራርተዋል። በመጠለያ ጣቢያ  ውስጥ ከሚገኙት በተጨማሪም በየጊዜው ከሱዳን የሚሻገሩ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በኅብረተሰቡ ውስጥ ተቀላቅሎ እንደሚገኙም ተናግረዋል። ተቋማቸው ለሁለተኛ ዙር ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ነሐሴ 18 ቀን 2015 ዓ.ም ድጋፍ ማድረሱን ተናግረዋል።

ፎቶ ከማኅደር፤ ቻድ ውስጥ ስደተኞችን ለመርዳት የተሰማራ የበጎ ፈቃድ ሠራተኛ
ከሱዳን የእርስ በርስ ጦርነቱን የሚሸሹ ወገኖች ወደ አጎራባች ሃገራት መሰደዳቸው ቀጥሏል። ፎቶ ከማኅደር፤ ቻድ ውስጥ ስደተኞችን ለመርዳት የተሰማራ የበጎ ፈቃድ ሠራተኛ ምስል ZOHRA BENSEMRA/REUTERS

በመተከል ዞን ጉባ ወረዳ በኩል ደግሞ ከ17 ሺህ በላይ የሚሆኑት ከዚህ ቀደም ከኢትዮጵያ ወደ ሱዳን የተፈናቀሉ ዜጎች መመለሳቸውን አመልክተዋል። እነዚህ የተመለሱ ዜጎች ከዚህ ቀደም በዞኑ የነበረው የጸጥታ ችግር ሸሽተው ሱዳን ውስጥ እንደነበሩ ገልጸዋል። የሱዳን ግጭት በመሸሽ ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የገቡ ዜጎችን ቁጥር መጨመርን ተከትሎ ሰብአዊ ድጋፍ ለማደረስ የለጋሽ ድርጅቶች እገዛ እንደሚያሰፈልገም አክለዋል። በሱዳን ውጥ ጦርነት ከተሰከተ ጊዜ አንስቶ ግጭቱን የሸሹ ሰዎች በአማራ ክልል፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እና ጋምቤላ በኩል ወደ ኢትየጵያ እየሸገሩ እንደሚገኙ የመንግሥታቱ ድርጅት መረጃ ያስረዳል። ከጠቅላላ ወደ ኢትጵያ ከመጡት መካከል አብዛኞቹ በመተማ በኩል ድምበር አቋርጠው የገቡ መሆናቸወን ዘገባው አመልክቷል። 

ነጋሳ ደሳለኝ

ሸዋዬ ለገሠ

ነጋሽ መሐመድ